የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ለእኛ ድኅነት እንደሆነ ቅዱስ መጽሐፉ ያስረዳል። ስለዚህ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሰፊው አብራርቶልናል። “የሰው ልጅ በራሱ ጥፋት በሞት ጥላ ሥር ቢወድቅም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በሞቱ ደምስሶ ለሚያምኑበት ሕይወትን ድኅነትን አውጇል። “አሁን ግን ክርስቶስ ለአንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተለይቶ ከሞት ተነስቶአል።” (፩ኛ ቆሮ.፲፭፥፳-፳፩) ሐዋርያውና ወንጌላዊው ማቴዎስ እንደጻፈው ኢየሱስ እኛን ከድካማችን ሁሉ ለማሳረፍ በእርሱም ዘንድ እረፍትን እንድናገኝ በቃሉ እንደጋበዘን ሲያስረዳን “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ” (ማቴ. ፲፩፥፳፰) እያለ ጥሪውን ያስተላልፋል። ስለዚህ ቤተክርስቲያናችንም ይህንን ቅዱስ ቃል መርሆ በማድረግ ወደ እግዚአብሔር ቤት ምዕመናንን በየጊዜው ትጋብዛለች። አሁንም እንኳን ለብርሃነ ትንሣዔው በሰላምና በሕይወት አደረሳችሁ እያልን እርስዎ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣዔና ሕይወት ተካፋይ እንዲሆኑ በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ስም ጥሪ እናቀርባለን። ይህም ጥሪ የእግዚአብሔር እንጂ ከሰው እንዳይደለ ክፍ ብሎ ተገልጿል። የእግዚአብሔርንም ጥሪ የተቀበሉ በእርሱ የሚመሩ በደስታ ይኖራሉ። የፈለጉት ሁሉ ይፈጸምላቸዋል። ይህንንም ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ሲል ያረጋግጣል። “ከእናንተ መካከል ጥበብ የጎደለው ቢኖር ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን ለእርሱም ይሰጠዋል። ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን።” (የያዕቆብ መልዕክት ፩፥፭-፯) ስለሆነም በዓሉ የበረከት የሰላምንና ፍቅርን በዓል ይሁንልዎ።
ሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ
በካናዳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ።
“አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል። ሞት በሰው በኩል ስለመጣ ትንሣዔ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።” (፩ኛ ቆሮ.፲፭፥፳-፳፩)
“But as it is, Christ is now raised from the dead, the first fruits of those who have fallen asleep. (1 Corinthians 15:20-21)
የትንሣዔ ፕሮግራም ቅዳሜ ሚያዚያ ፯ ቀን ፪ሺህ፱ ዓ.ም. ከምሽቱ ፲፪ ሰዓት እስከ ሌሊቱ ፯ ሰዓት ተኩል ድረስ ያካሄዳል።
EASTER CELEBRATION APRIL 15 tO April 16, 2017 FROM 6:00 PM TO 1:30 AM.
6:00 p.m. Gospel Sermon.
8:30 p.m. Opening prayer followed by Mahelet Debteras Liturgical Hymns
9:30 p.m. Prayer of the Gospel
Then the Lord awaked as one out of sleep, and like a mighty man that shouteth by reason of wine. And smote his enemies in the hinder parts: he put them into perpetual reproach. (Psalms 78: 65 - 66)
The Gospel of St. Matthew 28: 1 - 15
The Debters will continue Liturgical Hymns (Angeeragary and Esmelealem.)
At this time the congregation shall light the candles and chant after the deacons.
Youth choir present Werebe.
10:15 p.m. Prayer of the Covenant
10:30 p.m. The Divine Liturgy Service begun
Readings: 1 Corinthians 15: 20 – 41
1 Peter 1: 1 – 13
Acts 2: 22 – 37
Misbak Psalms 78: 65 – 66
Gospel The Gospel of St. John 20: 1 – 19
1:30 a.m. Closing prayer and dismissal.